ሰኔ 20 2017
የእስራኤልና ኢራን ግጭት፣ በኢትዮጵያ ወጪ ንግድ ላይ የሚኖረው ተፅዕኖ ምንድን ነው?
ባለሞያዎች ግጭቱ በንግግር መፍትሄን ካላገኘና የተራዘመ ከሆነ በዚህ ተጎጂ ከሚሆኑ ሀገራት ውስጥ ኢትዮጵያ አንዷ ልትሆን ትችላለች ይላሉ።
ዓለም የሀገራትን ንግድና ኢኮኖሚ ለረበሸው፣ የሩሲያ እና ዩክሬይን ጦርነት መቋጫ ሳታበጅ የኢራንና እስራኤል ግጭት ተከትሏል።
ቀጥተኛ የተኩስ ልውውጡ ከሰሞኑ በስምምነት ጋብ ቢልም፣ በአካባቢው ያለው ውጥረትና ስጋት ግን ባለበት ነው።
ልክ እንደተቀረው አለም ሁሉ፣ የሩስያ እና ዩክሬይን ጦርነት ብዙ ምርቶችን ከዚያ የምትሸምተውን የኢትዮጵያ ገበያም መረበሹን ባለሙያዎች በተደጋጋሚ ሲያነሱ ይሰማል።
አሁን ውጥረት ውስጥ የገባው የመካከለኛው ምስራቅ አከባቢም፣ ከነዳጅ ባለፈ የኢትዮጵያ ብዙ ምርቶች መዳረሻ መሆኑን የሚያነሱት በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት መሪ ተመራማሪ የሆኑት ዳርስከዳር ታዬ(ዶ/ር) ናቸው። እርሳቸው እንደሚሉት ኢትዮጵያን ጨምሮ የተቀረውን ዓለም ሁሉ የጎዳው የሩሲያ እና ዩክሬን ጦርነት መቋጫ ሳያገኝ የኢራንና እስራኤል ውጥረት መከተሉ በዓለም ዙሪያ ያለውን የንግድ ልውውጥ የበለጠ የሚረብሽ ነው። በዚህ ተጎጂ ከሚሆኑት ቀዳሚ ሀገራት ውስጥ ደግሞ ኢትዮጵያም አለችበት ብለዋል።
Comments