በኦሞ ወንዝና በቱርካና ሃይቅ መሙላት ምክንያት የመዋጥ አደጋ ላይ ያለችው የኦሞራቴ ከተማ
TRACK

በኦሞ ወንዝና በቱርካና ሃይቅ መሙላት ምክንያት የመዋጥ አደጋ ላይ ያለችው የኦሞራቴ ከተማ

Avatar

ነሀሴ 19 2017

በኦሞ ወንዝና በቱርካና ሃይቅ መሙላት ምክንያት የመዋጥ አደጋ ላይ ያለችው የኦሞራቴ ከተማ ታሪክ ልትሆን ተቃርባለች ተባለ፡፡

የደቡብ ኦሞ ዞን ዋና ከተማ የሆነች የኦሞራቴ ከተማ ከዓመት ዓመት በቱርካና ሃይቅ እና በኦሞ ወንዝ መሙላት ምክንያት የመዋጥ ስጋት እንዳለባት ሲነገር ቆይቷል፡፡

ከተማዋን የተጠጋት ውሃ ዘልቆ እንዳይገባ ጊዜያዊ መከላከያ ግድብ ቢሰራም ውሃው በከፍተኛ መጠን እየመጣ በመሆቡ ግድቡን ጥሶ ከተማዋን እንዳያጥለቀልቃት ስጋት ውስጥ ነን ያሉን የዞኑ አደጋ ስጋት ቢሮ ምክትል ሃላፊ ኞክ ኛንጋ ሞሮኜ ናቸው፡፡

በ2017 ዓ/ም መጀመሪያ የመስከረም ወር አካባቢ በአቅራቢያ ያሉ የደቡብ ኦሞ ወረዳዎችን ውጦ በማስቀረት ወደ ዋና ከተማዋ ኦሞራቴ ለመድረስ የ1.5 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የነበረው የቱርካና ሃይቅ ሙላት አሁን በጥቂት መቶ ሜትሮች ላይ ነው ያለው ተብሏል፡፡

Comments

Avatar