የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢትዮጵያን ጨምሮ ወደ ሀገራቸው ምርቶቻቸውን በሚልኩ 100 ሀገራት ላይ ለጣሉት ታሪፍ
TRACK

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢትዮጵያን ጨምሮ ወደ ሀገራቸው ምርቶቻቸውን በሚልኩ 100 ሀገራት ላይ ለጣሉት ታሪፍ

Avatar

ሐምሌ 22 2017

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢትዮጵያን ጨምሮ ወደ ሀገራቸው ምርቶቻቸውን በሚልኩ 100 ሀገራት ላይ ለጣሉት ታሪፍ የንግድ ሚዛን ጉድለትን እንደ ምክንያት ማቅረባቸው ይታወሳል።

እነዚህ ሀገራት ከአሜሪካ ከሚገዙት ይልቅ ወደ አሜሪካ የሚልኩት ምርት ይበልጣል የሚል ምክንያት ሰጥተዋል።

አንድ የምጣኔ ሃብት ባለሞያ ግን ይህ ምክንያት ኢትዮጵያን አይመለከትም፤ ውሳኔውን ለማስቀየርም መረጃን መሰረት ያደረገ ውይይት ከአሜሪካ ጋር መቀመጥ ያስፈልጋል ብለዋል።

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢትዮጵያን ጨምሮ ወደ ሀገራቸው ምርቶቻቸውን በሚልኩ 100 ሀገራት ላይ ታሪፍ ጥለዋል።

በኢትዮጵያ ላይ የተጣለው የ10 በመቶ ታሪፍ ነው።

ትራምፕ በሀገራቱ ላይ ታሪፉን የጣልኩት ከአሜሪካ ጋር ያላቸው የንግድ ሚዛን የተዛባ ስለሆነ ነው የሚል ምክንያት ሰጥተዋል።

ሀገራቱ ከአሜሪካ ከሚያስገቡት ይልቅ የሚልኩት ስለሚበልጥ የንግድ ሚዛን መዛባት ተፈጥሯል ብለዋል።

ታሪፉን ለመጣል የሰጡት ምክንያት አሳማኝ እንዳልሆነ የምጣኔ ሃብት ባለሞያው ዶክተር ታደለ ፈረደ ተናግረዋል።

በንግድ ልውውጡ እንዲያውም ተጎጂዋ ኢትዮጵያ ነች ብለዋል።

Comments

Avatar