ሐምሌ 17 2017
በደቡብ ምዕራብ ህዝቦች ክልል የመሬት መንሸራተት ቤቶችን እያፈራረሰ፣ ሰዎችን እያፈናቀለ መሆኑ ተሰማ፡፡
ከፋ፣ ቤንች ሸኮ ችግሩ ከደረሰባቸው የክልሉ ዞኖች መካከል ሲሆኑ የመሬት መንሸራተት ስጋት ያለባቸው ሌሎች አካባቢዎችም አሉ ተብሏል፡፡
ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በ20 ቀበሌዎች ላይ የመሬት መንሸራተት አደጋ መድረሱ ተነገረ፡፡
በክልሉ 80 መኖሪያ ቤቶች መውደማቸው በ23.7 ሄክታር መሬት ላይ ያለሰብል ላይም ጉዳት መድረሱ ተነግሯል፡፡
በሌሎች 30 ወረዳዎች ላይም ስጋት መሆኑንና በዚህም 49 አባወራዎች ከቤት ንብረታቸው እንደተፈናቀሉ ከክልሉ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ሰምተናል፡፡
Comments