ነሀሴ 1 2017
በኢትዮጵያ በካንሰር ምክንያት ከሚከሰተው ሞት 1.5 በመቶ የሚሆነው በሳምባ ካንሰር የሚመጣ ነው ተባለ፣ ነገር ግን ቁጥሩ በታወቁ የህክምና ተቋማት የተመዘገበ እንጂ ከዚህም ሊልቅ እንደሚችል ተነግሯል፡፡
በሀገሪቱ በዓመት ከ80,000 በላይ ሰዎች በተለያዩ የካንሰር ዓይነቶች ህይወታቸውን ያጣሉ ተብሏል፡፡
ቅድመ መከላከል በተለይም ምርመራና ህመሙ ሳይባባስ መለየቱ ላይ በብርቱ ስላልተሰራበትም በኢትዮጵያ በካንሰር ምክንያት የሚመዘገበው የሞት መጠን እየጨመረ መምጣቱን ጥናት አሳይቷል፡፡
የሳምባ ካንሰርን በተመለከተ ያለውን ሀገራዊ መጠን ለማወቅ የኢትዮጵያ ቶራሲክ ሶሳይቲ የተለያዩ ምርምሮችን እያካሄደ መሆኑን ተናግሯል፡፡
Comments