ሐምሌ 16 2017
ዛሬ ላይ በኢትዮጵያ የሚገኙ አብዛኞቹ የህብረት ስራ ማህበራት ከብዙ ዓመታት በፊት መቶ ብር እና ከዚያ በታች በሆኑ ትናንሽ የግለሰቦች የገንዘብ መዋጮ የተቋቋሙ ናቸው።
ተግባራቸው እንደ ተደራጁበት ዓላማ ቢለያይም የአብዛኞቹ የምርት አቅርቦትን በማሳደግ ገበያን ማረጋጋት ነው።
ይህን ሲያደርጉ አምራቹ ትክክለኛውን ዋጋ ያገኛል፤ ሸማቹም ጥራት ያለው ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ ይገዛል ተብሎ ይታሰባል።
ይህን ዓላማ ከማሳካት አንፃር ምንም አልሰሩም ባይባልም የታሰበውን ያህል ናቸው ለማለትም እንደሚከበድ የኢትዮጵያ ህብረት ስራ ኮሚሽን ይናገራል።
ኮሚሽኑ እንደሚለው የብቃት እና የተወዳዳሪነት ማነስ፣ የሃብት ብክነትና ዘረፋ እንዲሁም እንደ ፋይናንስ እጥረት ያሉ ችግሮች በማህበራቱ ላይ ታይተዋል።
Comments